በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የቡድን 20 አባል አገሮች ጉባኤ ተጀመረ


ዛሬ ጣልያን ሮም ውስጥ በተመጀመረው የቡድን 20 አባል አገራት ጉባኤ ላይ የተገኙ የዓለም መሪዎች
ዛሬ ጣልያን ሮም ውስጥ በተመጀመረው የቡድን 20 አባል አገራት ጉባኤ ላይ የተገኙ የዓለም መሪዎች

የበለጸጉ አገራት መሪዎች የኮቪድ 19 ወረርሽኝና የአየር ንብረት ለውጥን ጨምሮ፣ በሚያሳስቧቸው የጋራ ጉዳዮች ለመነጋገር፣ ዛሬ ቅዳሜ ጣልያን ሮም ውስጥ በተመጀመረው የቡድን 20 አባል አገራት ጉባኤ ላይ ተገኝተዋል፡፡

በሮም የኮንቬንሽ ሴንተር በሚካሄደው ስብሰባ የጣልያን ጠቅላይ ሚኒስትር ማርዮ ድራጊ፣ የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ጆ ባይደንን ጨምሮ፣ ሌሎች መሪዎችን የኮቪድ 19 ፕሮቶኮል በሚፈቅደው መሠረት ተቀብለዋል፡፡

መሪዎቹ ከሁለት ዓመት በኋላ በአካል ሲገናኙ ይህ የመጀመሪያቸው ነው፡፡

በስብሰባው ላይ የቻይናው ፕሬዚዳን ጂ ፒንግ፣ የሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን እና የሜክሲኮ ፕሬዚዳንት አንድሬስ ማኑኤል ሎፔዝ ኦርባዶር በአካል ያልተገኙ ሲሆን ስብሰባውን በድረገጽ እንደሚሳተፉ ተገልጧል፡፡

XS
SM
MD
LG