በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ከመንፈቅ ዓመቱ የእሳት አደጋዎች 94 በመቶ በአዲስ አበባ የደረሱ ናቸው


ከመንፈቅ ዓመቱ የእሳት አደጋዎች 94 በመቶ በአዲስ አበባ የደረሱ ናቸው
please wait

No media source currently available

0:00 0:07:28 0:00

ከመንፈቅ ዓመቱ የእሳት አደጋዎች 94 በመቶ በአዲስ አበባ የደረሱ ናቸው

በኢትዮጵያ ባለፉት ስድስት ወራት ውስጥ ብቻ በደረሰው የእሳት አደጋ ወደ ግማሽ ቢሊዮን ብር ንብረት መወደሙ ተገለጸ።

በዚህ ዓመት ስድስት ወራት ውስጥ 139 የእሳት ቃጠሎዎች በሀገር አቀፍ ደረጃ መድረሳቸውን ለአሜሪካ ድምፅ የተናገሩት የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ጄይላን አብዲ፣ መንሥኤያቸውንም በፎረንሲክ ምርመራ ለመለየት እንደተቻለ ገልጸዋል።

ከእሳት ቃጠሎዎቹ 94 በመቶዎቹ በአዲስ አበባ መድረሳቸውን የጠቀሱት የእሳት እና አደጋ ሥራ አመራር ኮሚሽን የሕዝብ ግንኙነት ባለሞያ አቶ ንጋቱ ማሞ፣ ግማሽ ቢሊዮን ብር ገደማ ሀብትም በአደጋው መውደሙን ተናግረዋል።

በጉዳዩ ላይ፣ ዘጋቢያችን በቅርቡ በእሳት ቃጠሎ ቤታቸው የወደመባቸውን የአዲስ አበባ ነዋሪንም አነጋግሮ ተከታዩን ዘገባ አዘጋጅቷል፡፡

መድረክ / ፎረም

XS
SM
MD
LG