ዋሽንግተን ዲሲ —
የሰብዓዊ መብት ጥሰት ጥያቄውን ለመመለስ የፌደራል ማረሚያ ቤቶች አመራሮች ተነስተው በአዲስ መተካታቸውን የፌደራል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ አስታወቀ።
የዓለም አቀፉ የሰብዓዊ መብት ተከራካሪ አምነስቲ ኢንተርናሽናል የአፍሪካ ቀንድ ተመራማሪ አቶ ፍሰኃ ተክሌ፤ ድርጅታቸው በኢትዮጵያ የሚፈፀሙ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን በተመለከተ ባሰባሰበው ሪፖርት፤ ዘግናኝ የሆኑ ምርመራዎች የተፈፀሙት በስፋት መሆኑን ፤ የሚፈፀሙባቸው እርስ ቤቶች ደግሞ የተዘጋውን ማዕከላዊ ጨምሮ በኦሮሚያ ክልል፣ በአማራ ክልል፣ በሶማሌ፣ በደቡብ እና በሌሎች ባልታወቁ እስር ቤቶች ጭምር እንደሚፈፀሙ ተናግረዋል።
እነዚህን አሰቃቂ ወንጀሎች በዜጎች ላይ የፈፀሙ ሰዎች ለፍርድ ሊቀርቡ ይገባል፣ ተጎጂዎቹ ካሳ ሊሰጣቸውና በዘላቂነት ሊቋቋሙ ይገባል ብለዋል።
ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።
የፌስቡክ አስተያየት መስጫ