በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የአቶ አንዳርጋቸውን መሰጠት የሚቃወሙ ሰልፎች ተደረጉ


የኢትዮጵያዊያኑ የተቃውሞ ሰልፍ የመን ኤምባሲ ደጃፍ ላይ - ዋሺንግተን ዲሲ
የኢትዮጵያዊያኑ የተቃውሞ ሰልፍ የመን ኤምባሲ ደጃፍ ላይ - ዋሺንግተን ዲሲ

please wait

No media source currently available

0:00 0:10:28 0:00
ቀጥተኛ መገናኛ

የግንቦት ሰባት ዋና ፀሐፊ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ሰንዐ - የመን ላይ ተይዘው ለኢትዮጵያ ተላልፈው መሰጣታቸውን በመቃወም ዋሺንግተን ዲሲ እና በአባባቢዋ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ-ኢትዮጵያ አሜሪካዊያን የመን ሪፐብሊክ ኤምባሲ ደጃፍ ላይ የተቃውሞ ሰልፍ አድርገዋል፡፡

የመን ኤምባሲ ደጃፍ ላይ የተገኙት ኢትዮጵያዊያን የመን አቶ አንዳርጋቸውን አሳልፋ መስጠቷ ያስቆጣቸው መሆኑን አሳውቀዋል፡፡

ሰልፈኞቹ ከኤምባሲው የሚወጡና የሚገቡ ተሽከርካሪዎችና ሠራተኞችን በብዙ ድምፅ፣ ጩኸትና መፈክር አውከዋል፡፡ የመን ሽብርተኛ፣ ሃፍረት ለእናንተ የሚሉ መፈክሮችን አሰምተዋል፡፡

ሰልፈኞቹ የየመንን ባንዲራና የፕሬዚዳንቷን ፎቶ አቃጥለዋል፡፡

ለዝርዝሩ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡

XS
SM
MD
LG