በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ለመንግሥት “ማስጠንቀቂያ” እየሰጠን ነው ያሉ የኢትዮጵያ ሙስሊሞች አደባባይ ዋሉ


“ቢጫ ጁምዓ”
“ቢጫ ጁምዓ”

የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ዕሁድ መስከረም 27 ቀን 2005 ዓ.ም የሚካሄደውን የእስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ምርጫ በመቃወም ዓርብ መስከረም 25 ቀን 2005 ዓ.ም ከጁምዓ ሶላት ጋር ተያይዞ በዋና ከተማይቱ አዲስ አበባና ሌሎችም ከተሞች ውስጥ ተቃውሞ አሰምተዋል።



please wait

No media source currently available

0:00 0:18:14 0:00
ቀጥተኛ መገናኛ

please wait

No media source currently available

0:00 0:14:27 0:00
ቀጥተኛ መገናኛ


ብዙ ሙስሊሞች መንግሥት በምርጫዎቹ ጣልቃ እየገባ ነው ብለው እንደሚያምኑ ከአዲስ አበባ ይሰማል፡፡

የተቃውሞው ትዕይንት የተካሄደው በአዲስ አበባና በሌሎችም ከተሞች መሆኑ የተሰማ ሲሆን በአዲስ አበባው አንዋር መስጊድ የተገኙት በብዙ ሺሆች የሚቆጠሩ ሠልፈኞች ቢጫ ካርድ ይዘው “ድምፃችን ይሰማ”፤ “ዋ! ዋ!” ይሉ ነበር፡፡

አንዋር መስጊድ እና አካባቢው፤ ዓርብ፣ መስከረም 25/2005 ዓ.ም
አንዋር መስጊድ እና አካባቢው፤ ዓርብ፣ መስከረም 25/2005 ዓ.ም

በሌላ በኩል ደግሞ ምርጫው የሚፈፀመው በሙስሊሙ ኅብረተሰብ ዕውቅና ባልተሰጣቸው ሰዎች ነው በሚል እንዲታገድላቸው ፍርድ ቤትን ለመጠየቅ የሞከሩ የሙስሊሙ ኅብረተሰብ ቅሬታዎች መፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት ጠበቃ አቤቱታቸውን ፍርድ ቤት እንደማይቀበል አስታውቀዋል፡፡

የኮሚቴው አባላት የሚገኙት በእሥር ላይ እንደሆነ ይታወቃል፡፡

የቪኦኤ ዘጋቢዎችን ሪፖርቶች ያዳምጡ፡፡
XS
SM
MD
LG