በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የኢትዮጵያ ጦር ኤል-አሊ ከተማን ለቅቆ ወጣ


አሚሶም - ኢትዮጵያ/ፎቶ ፋይል
አሚሶም - ኢትዮጵያ/ፎቶ ፋይል

ሶማሊያ ውስጥ የሚገኘው የኢትዮጵያ ጦር ከማዕከላዊቱ ሂራን ክልል ኤል-አሊ ከተማ ለቅቆ መውጣቱ ተገለፀ፡፡

ሶማሊያ ውስጥ የሚገኘው የኢትዮጵያ ጦር ከማዕከላዊቱ ሂራን ክልል ኤል-አሊ ከተማ ለቅቆ መውጣቱ ተገለፀ፡፡

የጦሩን መውጣት ተከትሎ የአል-ሻባብ ተዋጊዎች ከተማዪቱን መቆጣጠራቸው ታውቋል፡፡

ኢትዮጵያዊያኑ ወታደሮች ይዞታዎቻቸውን ሲለቅቁ እዚያቹ ሂራን ክልል ውስጥ በቁጥጥራቸው ሥር ከነበሩ ከተሞች መካከል ኤል-አሊ ሁለተኛ መሆኗ ነው፡፡

ሰሞኑን ኤል-አሊ አቅራቢያ በምትገኝ ሞቆኮሪን እንዲሁ ለቅቀው መውጣታቸውን የኬንያው ዴይሊ ኔሽን ጋዜጣ ዘግቧል፡፡

የኢትዮጵያ ወታደሮች ዛሬ ማለዳ ከለቀቋት ኤል-አሊ ለምን እንደወጡ ለጊዜው ዝርዝር ማግኘት ባይቻልም የእንግሊዝ የዜና ወኪል - ቢቢሲ የአል ሻባብን ራዲዮ አንዳሉስን ጠቅሶ ባሠራጨው ዜና ጦሩ ሠፍሮበት የነበረው መደብ መደብደቡን አመልክቷል፡፡

በሶማሊያ የአፍሪካ ኅብረት ጦር - የአሚሶም አካል የሆነው የኢትዮጵያ ሠራዊት ኤል አሊ ከተማን ለቅቆ መውጣቱን የከተማዪቱ ከንቲባ አደን አሊ ፊዶው ለቪኦኤ በሰጡት ቃል አረጋግጠዋል፡፡

ለተጨማሪ የተያያዘውን ድምፅ ያዳምጡ።

የኢትዮጵያ ጦር ኤል-አሊ ከተማን ለቅቆ ወጣ
please wait

No media source currently available

0:00 0:01:52 0:00

XS
SM
MD
LG