በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የሽብር ክሥ የተመሠረተባቸው በነፃ ተለቀቁ


ፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት
ፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት

እንዲከራከሩ ብይን የተሰጣቸው የሕግ ድንጋጌ እንዲለወጥ ታዘዘ፤ በሙስና የተከሰሱ ጉዳይም ታይቷል፡፡




የሽብር ፈጠራ ክሥ ተመሥርቶባቸው የታሠሩ የሙስሊሙ ኅብረተሰብ ጥያቄ መፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት
የሽብር ፈጠራ ክሥ ተመሥርቶባቸው የታሠሩ የሙስሊሙ ኅብረተሰብ ጥያቄ መፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት

please wait

No media source currently available

0:00 0:08:09 0:00
ቀጥተኛ መገናኛ


እንዲከራከሩ ብይን የተሰጣቸው የሕግ ድንጋጌ እንዲለወጥ ታዘዘ፤ በሙስና የተከሰሱ ጉዳይም ታይቷል፡፡

አቶ ተማም አባቡልጉ - የሕግ ባለሙያ
አቶ ተማም አባቡልጉ - የሕግ ባለሙያ
የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ አራተኛ ወንጀል ችሎት በሽብር አድራጎት ተከስሰው ከነበሩት የሙስሊሙ ማኅበረሰብ ጥያቄዎች መፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላትና ሌሎች ተከሣሾች መካከል አሥር ሰዎችና ሁለት ድርጅቶች መከላከል ሳያስፈልጋቸው በነፃ አሰናበተ፡፡

ሌሎቹን ተከሣሾች የተከሰሱባቸው የሕግ ድንጋጌዎች ተለውጠው እንዲከላከሉ ብይን ሰጥቷል፡፡

ፌደራል የሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን
ፌደራል የሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን
15ኛ ወንጀል ችሎት ደግሞ በሙስና ወንጀል የተከሰሱትን የአቶ መላኩ ፈንታን ጉዳይ “የሚያየው ፍርድ ቤት የቱ ነው” በሚለው ጥያቄ ላይ የመጨረሻውን ውሣኔ ለማሰማት ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

ከነአቶ መላኩ ፈንታ ጋር የተከሰሱት የቀድሞ የሃገር ውስጥ ደኅንነት ኃላፊ ተጨማሪ ክሦች ቀርበውባቸዋል፡፡

መለስካቸው አምሃ የዛሬን የፍርድ ቤት ውሎ ዝርዝር ዘገባ ይዟል፡፡
XS
SM
MD
LG