በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የአገር ጉዳይ:- ውይይት ዘለቄታ ባላቸውና የሁላችንም በሚሆኑ ግቦች ዙሪያ


“ግራ ቀኙን ያለውን ሁኔታ ስከታተለው ነበር። አሁን አገሪቱ የጭንቅ አማላጅ የምትፈልግበት ሰዓት ነው። በፖለቲካውም ጎራ ከዚህ ቀደም ያልተለመዱ ሁኔታዎች እያየን ነው።” ዲያቆን ዳንኤል ክብረት። “ኢትዮጵያ በጣም ፈታች ሁኔታ ላይ እንዳለች ይሰማኛል። የአለቃ አያሌውን ግግግር ተውሼ፣ መልህቋን የምትጥልበት አጥታ ማዕበል ከወዲህ ወዲያ በሚያላጋት በውል ለመለየት ከሚቸግር አደገኛ ሁኔታ ላይ እንዳለች ይሰማኛል።” አቶ ሃብታሙ አያሌው።

“የአገር ጉዳይ”... ተመልሶ መጥቷል። የአንድ አገርና ሕዝብ ፈተናዎች፥ የመውጫ መንገዶችና ተሥፋ።

ትላንትናችንን፥ ዛሬንና ነገን፤ መንታ መንገድ ላይ ያለች በምትመስለው ሃገር ሰሞንኛ ይዞታ ውስጥ የሚደረግ የሃሳብ ቅኝት ነው። ራዲዮ መጽሔት ከዚህ ቀደም ይህን መሰል ሁኔታ ሲፈጠር በተለየ ትኩረት ያሰልስ እንዳደረገው ሁሉ ዛሬም አነጋጋሪ፥ አሳሳቢና ሁነኛ መላ ለሚሹት አንገብጋቢ የአገርና የሕዝብ ጉዳዮች ገጾቹን ገልጧል።

በኢትዮጵያ ጉዳዮች የሚጽፉ፥ በተለያዩ መንገዶች በንቃት የሚሳተፉና በሚጠበቡባቸው የሞያ መስኮች ለብዙዎች ጥቅም የሚውሉ ሥራዎቻቸው የሚታወቁ፤ የሕዝብ ጉዳይ ግድ የሚላቸውን የማኅበረሰብ አባላት ማነጋገሩን ቀጥለናል።

በኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ ባተኮሩ ምሁራዊ ጽሁፎቹ በሥፋት የሚታወቀውና መንፈሳዊ ይዘት ያላቸው በርካታ መጽሃፍት ደራሲው ዲያቆን ዳንኤል ክብረት እና በፖለቲካ ተሳፎው ሳቢያ ለበረታ እንግልት ቢዳረግም ዛሬም ከኢትዮጵያ ጉዳዮች ያልራቀው
የቀድሞው የአንድነት የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ሃብታሙ አያሌው ለውይይቱ ተሰይመዋል።

እርሶም የዚህ ተከታታይ ውይይት ተሳታፊ ይሆኑ ዘንድ ተጋብዘዋል። አድማጮች በያላችሁበት ከምታደርጉት ውይይት በተጨማሪ ለአገርና ለሕዝብ ይበጃሉ የምትሏቸውን አዎንታዊ ሃሳቦች አድርሱን።

ውይይቱን ከዚህ ያድምጡ፤

የአገር ጉዳይ:- ውይይት ከዲያቆን ዳንኤል ክብረትና ሃብታሙ አያሌው ጋር .. ክፍል አንድ
please wait

No media source currently available

0:00 0:11:41 0:00
የአገር ጉዳይ:- ውይይት ከዲያቆን ዳንኤል ክብረትና ሃብታሙ አያሌው ጋር .. ክፍል ሁለት
please wait

No media source currently available

0:00 0:14:29 0:00

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG