በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የናይሮቢው ውይይት ቀጥሏል


የናይሮቢው ውይይት ቀጥሏል
please wait

No media source currently available

0:00 0:07:02 0:00

የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት እና የህወሓት ወታደራዊ አዛዦች በናይሮቢ እያደረጉት ያለው ውይይት እስከ ነገ ሊቀጥል እንደሚችል የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።

የተለያዩ ሃገሮችና ዓለም አቀፍ ተቋማት፣ ለሰላም ሥምምነቱ ተግባራዊነት እንዲሁም ለመልሶ ማቋቋም እና የመልሶ ግምባታ ሥራዎች ድጋፍ እንደሚያደርጉ እየነገሯቸው መሆኑን የሚኒስቴሩ ቃል አቀባይ አምባሳደር መለስ ዓለም ዛሬ በሰጡት መግለጫ አስታውቀዋል።

ከተዋዋይ ወገኖች ጋር ተባብረን መሥራታችንን እንቀጥላለን ያሉት የዩናይትድ ስቴትስ ውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ቃል አቀባይ ኔድ ፕራይስ ደግሞ፣ የሥምምነቱ ቀጣይ ተፈጻሚነት ወሳኝ ነው ብለዋል፡፡

/ዝርዝር ዘገባውን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ/

XS
SM
MD
LG