በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

 
በእነ አቶ ዮሐንስ ቧያሌው መዝግብ ከተከሰሱት ውስጥ የተወሰኑት በፍርድ ቤት ተከራከሩ 

በእነ አቶ ዮሐንስ ቧያሌው መዝግብ ከተከሰሱት ውስጥ የተወሰኑት በፍርድ ቤት ተከራከሩ 


የምክር ቤት አባል የሆኑት አቶ ዮሐንስ ቧያለው እና አቶ ክርስቲያን ታደለ
የምክር ቤት አባል የሆኑት አቶ ዮሐንስ ቧያለው እና አቶ ክርስቲያን ታደለ

በአማራ ክልል በመንግስት የፀጥታ ኃይሎች እና በፋኖ ታጣቂዎች መሀል ከቀጠለው ግጭት ጋር በተያያዘ፣ በእነ አቶ ዮሐንስ ቧያሌው መዝግብ የሽብር ክስ ከተመሰረተባቸው 52 ተከሳሾች መካከል 16ቱ ዛሬ በፍርድ ቤት ቀርበው፣ ወንጀሉን አለመፈፀማቸውን በመግለፅ ተከራክረዋል። ተከሳሾቹ የእምነት ክህደት ቃላቸውን የሰጡት፣ "የአማራን ክልል መንግሥት በኃይል ከሥልጣን ለማውረድ" ሞክራችኃል በማለት የቀረበባቸውን ክስ ተቃውመው ሲከራከሩ መቆየታቸውን ተከትሎ ዓቃቤ ሕግ ዛሬ የተሻሻለውን ክስ ለፍርድ ቤት ከአቀረበ በኋላ ነው።

በእነ አቶ ዮሐንስ ቧያሌው መዝግብ ከተከሰሱት ውስጥ የተወሰኑት በፍርድ ቤት ተከራከሩ 
please wait

No media source currently available

0:00 0:06:02 0:00

በአማራ ክልል በተከሰተው የፀጥታ ችግር ምክንያት ከታወጀው የአስቸኳይ ጊዜ ዐዋጅ ጋራ በተያያዘ ተከሳሾቹ በቁጥጥር ስር ውለው አዋሽ አርባ እና ሰመራ በሚገኘው የእስረኛ ማቆያ ለወራት በቆዩበት ወቅት ደርሶብናል ያሉትን የሰብአዊ መብት ጥሰት እንዲመረምር በፍርድ ቤቱ ታዞ የነበረው የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽንም የምርመራውን ውጤት ዛሬ ለፍርድ ቤቱ ያቀረበ ሲሆን፣ የሰብአዊ መብት ጥሰትን በፈፀሙ አካላት ላይ ምርመራ እንዲደረግ እና ተጠያቂነት እንዲኖር ምክረ ሐሳብ ማቅረቡን የተከሳሾች ጠበቃ አቶ ሰለሞን ገዛኸኝ ለአሜሪካ ድምፅ ገልፀዋል።

መድረክ / ፎረም

XS
SM
MD
LG