አዲስ አበባ —
የፊታችን ሰኞ የኢትዮጵያ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና የፌዴሬሽን ምክር ቤት አዲስ እንደራሴዎች ስራ የጀምራሉ። ሁለቱም የህግ አውጭ አካላት በገዥው ፓርቲ ኢህአዴግ መቶ በመቶ ቁጥጥር ስር የሚገኙ ናቸው።
ባለፈው ዓመት ግንቦት ወር በተካሄደው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምርጫ ኢህአዴግና አጋር ድርጅቶቹ 547ቱን መቀመጫዎች ሙሉ በሙሉ ተቆጣጥረዋል።
የጠቅላይ ሚኒስትር ምርጫ
ሰኞለት የሚሰየመው ፓርላማ የጠቅላይ ሚኒስትር ምርጫ የሚያከናውን ሲሆን፤ ገዥው ፓርቲ የሚመሰርተውን መንግስት ማለት የሚኒስትሮች ምክር ቤትም ተከትሎ ይቀርባል።
የኢትዮጵያ የፌዴሬሽን ምክርበትና የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በቀዳሚነት አፈ ጉባዔዎቻቸውን እንደሚመርጡ የወጣው የጊዜ ሰሌዳ ያስረዳል።