በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ለአሥር ወራት ተጥሎ የቆየው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ተነሣ


"አዋጁ መታወጅም ሆነ ለአሥር ወራት መቆየት አልነበረበትም" - ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ

ለአለፉት አሥር ወራት ተጥሎ የቆየው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ መነሳቱን የኢትዮጵያ መንግሥት አስታወቀ፡፡

“አዋጁ እንዲታወጅ መነሻ የነበሩ ሁኔታዎች በከፍተኛ ደረጃ እንዲቀንሱ ተደርገዋል” ብሏል፤ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ኮማንድ ፓስት ሲክሬታርያትና የመከላከያ ሚኒስትር ሲራጅ ፈጌሣ፡፡

Ethiopia State Of emergency
Ethiopia State Of emergency

​ሁከት፣ ብጥብጥ፣ ሽብር በመፍጠር ወንጀል የተጠረጠሩ ሰባት ሺሕ ሰባት መቶ ሠላሳ ሰባት ሰዎች ግን አሁንም በእሥር ላይ አንደሚገኙና በተለያዩ ፍርድ ቤቶች ክሳቸውን እየተከታተሉ እንደሚገኙ ገልፀዋል፡፡

አንጋፋው የተቃዋሚ ፓርቲ መሪ ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ ግን፣ አዋጁ መታወጅም ሆነ ለአሥር ወራት መቆየት አልነበረበትም ብለዋል፡፡

“የፍርኃትና የተፅዕኖ ድባብ፣ በሀገሪቱ ያሰፈነ ነበር” ሲሉም ነው የገለፁት፡፡

ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።

ለአሥር ወራት ተጥሎ የቆየው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ተነሣ
please wait

No media source currently available

0:00 0:07:53 0:00

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG