በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በጋዜጠኞቹና በብሎገሮቹ ላይ ክሥ ተመሠረተ


ፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት
ፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት

ለሦስት ወራት ያህል ክስ ሳይመሠረትባቸው ታስረው በቆዩት ዘጠኝ ጋዜጠኞችና የኢንተርኔት ፀሃፊዎች፤ እንዲሁም በአንድ ሌላ ተጠርጣሪ ላይ አቃቢ-ህግ ዛሬ የአሸባሪነት ክሥ ከፈተ።

የታሠሩት ብሎገሮችና ጋዜጠኞች /የፎቶ ምንጭ - ኢንተርኔት/
የታሠሩት ብሎገሮችና ጋዜጠኞች /የፎቶ ምንጭ - ኢንተርኔት/

please wait

No media source currently available

0:00 0:06:26 0:00
ቀጥተኛ መገናኛ

ለሦስት ወራት ያህል ክስ ሳይመሠረትባቸው ታስረው በቆዩት ዘጠኝ ጋዜጠኞችና የኢንተርኔት ፀሃፊዎች፤ እንዲሁም በአንድ ሌላ ተጠርጣሪ ላይ አቃቢ-ህግ ዛሬ የአሸባሪነት ክሥ ከፈተ።

ክሡ በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ችሎት ክሡ የተመሠረተባቸው በፈቃዱ ኃይሉ፤ ናትናኤል ፈለቀ፣ ማኅሌት ፋንታሁን፣ አጥናፉ ብርሃኔ፣ ዘላለም ክብረት፣ አቤል ዋበላ፣ አስማማው ኃይለጊዮርጊስ፣ ኤዶም ካሣዬና ተስፋለም ወልደየስ ሲሆኑ በአንደኛ ተከሣሽነት የተጠቀሰችው ሶልያና ሺመልስ የተከሰሰችው በሌለችበት ነው፡፡

ክሦቹ በንባብ ከተሰሙ በኋላ የተመሠረተው ክሥ በሽብር አዋጅ የቀረበ ስላልሆነ ተጠርጣሪዎቹ የዋስ መብታቸውን ሊነፈጉ አይገባም ሲሉ የተከሳሽ ጠበቆች ተከራክረዋል።

አቃቢ-ህግ ተቃውሟል፤ ፍርድ ቤት ብይን ለመስጠት ተለዋጭ ቀጥሮ ሰጥቷል።

ለዝርዝሩ የተያያዘውን ችሎቱ ላይ ተገኝቶ የነበረውን የመለስካቸው አምሃን ዘገባ ያዳምጡ፡፡

XS
SM
MD
LG