አዲስ አበባ —
መንግሥት ለሰብዓዊ መብቶች መከበርና ለዲሞክራሲ መስፈን ያለውን ቁርጠኝነት በተግባር እንዲያሳይ ሰመጉ ጠየቀ፡፡
ሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ በኢትዮጵያ ማዕከላዊ ወንጀል ምርመራን የመሳሰሉ አያሌ የዜጎች ማሰቃያ ስፍራዎች እንዳሉም ገልፆ ሁሉም በይፋ እንዲዘጉ አሳሰበ፡፡
የሀገሪቱን ቀውስ ለመፍታት ከሁሉም መቅደም አለባቸው ያላቸውን ርምጃዎችም ጠቁሟል፡፡
ሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ /ሰመጉ/ ታኅሣስ 27/2010 ዓ.ም አመሻሹ ላይ በኢንተርኔት ባሰራጨው ፁሑፍ፣ የሰብዓዊ መብቶች ተከራካሪ ድርጅት እንደመሆኑ መጠን ገዥው ግንባር ኢህ አዴግ በዚያው ሳምንት ቀደም ብሎ ባወጣው መግለጫ አስመልክቶ ያለውን አቋም ያስታወቀበት መግለጫ እንደሆነ አስታውቋል፡፡
ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።
የፌስቡክ አስተያየት መስጫ