በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ኃይለማርያም ደሣለኝ - ጠቅላይ ሚኒስትር


ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሣለኝ ቃለ መሃላ ፈፀሙ
ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሣለኝ ቃለ መሃላ ፈፀሙ

አዲሱ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሣለኝ የሃገሪቱን ምጣኔ ኃብት እና ምሥራቅ አፍሪካን በሚመለከት የቀደሙትን ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊን ፖሊሲዎች ይዘው እንደሚቀጥሉ አስታወቁ፡፡

please wait

No media source currently available

0:00 0:15:06 0:00
ቀጥተኛ መገናኛ



ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሣለኝ ዛሬ ቃለ መሃላ ከፈፀሙ በኋላ ለፓርላማው ባደረጉት ንግግር ኢትዮጵያ ብሩህ መጭ ጊዜ የሚጠብቃት መሆኑንና ድሕነት ሊሸነፍ የሚችልበት ደረጃ ላይ መድረሷን አመልክተዋል፡፡

ኃይለማርያም ደሣለኝ ከሃያ ዓመታት በዘለቀ ጊዜ ውስጥ የመጀመሪያው የኢትዮጵያ አዲስ ጠቅላይ ሚኒስትር መሆናቸው ነው፡፡

አቶ ኃይለማርያም ደሣለኝ በአንድ ወቅት፤ ምናልባትም የሁለት ዓመት ተኩል በፊት ይሆናል፤ ቀድሞ ያዲሳባ ዘጋቢያችን፣ የዛሬ የአፍሪካ ቀንድ ኃላፊ ፒተር ሃይንላይን ጋር ተከታታይ ቃለ-ምልልስ አድርገው ነበር፡፡

ያኔ በገዥው ፓርቲ ኢሕአዴግ ቃልአቀባይነታቸው ነበር ከፒተር ጋር የተወየዩት፡፡ በዚያ ውይይታቸው ያተኮሩት ኢሕአደግ ስለሚመራበት የአንድ ፓርቲ የበላይነት ፍልስፍና ሆኖ በዛሬው አዲሱ ሥልጣናቸው ስለሚያራምዱትም ፖሊሲ ፍንጭ ሰጥተዋል፡፡

የእስክንድር ፍሬውንና የፒተር ሃይንላይንን ዘገባዎች ያዳምጡ፡፡
XS
SM
MD
LG