በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

መድረክ አባሉ በደቡብ ኢትዮጵያ ተደብድበው መገደላቸውን ገለጸ


Merara Gudina and Beyene Petros of Medrek at a Press Conference in Addis Ababa May 2015
Merara Gudina and Beyene Petros of Medrek at a Press Conference in Addis Ababa May 2015
please wait

No media source currently available

0:00 0:06:36 0:00
ቀጥተኛ መገናኛ


የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ አንድነት መድረክ በደቡብ ክልል አንድ የምርጫ አስተባባሪው አርብለት ተገድለው መገኘታቸውን አስታወቀ። የተቃዋሚ ፓርቲም በምርጫ 2007 ዙሪያ የዛሬውን ጨምሮ 4 አባላቱና ደጋፊዎቹ መገደላቸውን አስታውቋል።

በዚህ ሳምንት እንደተገደሉ ተቃዋሚዎች ከገለጿቸው ሶስት ሰዎች በተጨማሪ በኦሮሚያና ደቡብ ክልል ህይወታቸው ማለፉ የተገለጸው አጠቃላይ ቁጥር ስድስት ደርሷል።

በደቡብ ክልል ሀዲያ ዞን ሶሮ ወረዳ የተገደሉት አቶ ብርሃኑ ኤረቦ በትናንትናውለት በሁለት ፖሊስ ባልደረቦች ከመኖሪያ ቤታቸው ከተወሰዱ በኋላ ተደብድበው ህይወታቸው አልፎ ወንዝ ዳር መገኘታቸውን የመድረክ ሊቀመንበር ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ ገልጸዋል።

በኢትዮጵያ ምርጫ 2005 በመላ ሀገሪቱ በሚገኙ ወደ 46ሽህ የሚጠጉ የድምጽ መስጫ ጣቢያዎች ሰላማዊ በሆነ መልኩ መከናወኑን የኢትዮጵያ መንግስትና ምርጫ ቦርድ ይገልጻሉ። የተቃዋሚ ፓርቲዎች ሂደቱ በወከባ እስራትና አልፎ አልፎ ግድያዎች የታዩበት ነው በሚል፤ ሂደቱንና ውጤቱን አንቀበለም በማለት መግለጫዎች አውጥተዋል።

XS
SM
MD
LG