በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

አወዛጋቢው የምርጫ 2007 አጠቃላይ ይፋ ውጤት እና የተቃዋሚዎች ምላሽ


የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ ሊቀ-መንበር ፕሮፌሰር መርጋ በቃና በግንቦርት ወረ ታካሂዶ የነበረውን ምርጫ ይፋ ውጤት አስታወቁ።
የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ ሊቀ-መንበር ፕሮፌሰር መርጋ በቃና በግንቦርት ወረ ታካሂዶ የነበረውን ምርጫ ይፋ ውጤት አስታወቁ።
አወዛጋቢው የምርጫ 2007 አጠቃላይ ይፋ ውጤት እና የተቃዋሚዎች ምላሽ
please wait

No media source currently available

0:00 0:15:07 0:00
ቀጥተኛ መገናኛ


ኢሕአዴግና አጋሮቹ የግንቦት 16ቱን ምርጫ 100 በመቶ ለማሸነፍና 547ቱንም የፓርላማ መቀመጫዎች ሙሉ በሙሉ ለመያዝ የአንድ የምርጫ ክልል ውጤት ብቻ ይጠብቃሉ።

የምርጫውን አጠቃላይ ውጤት ዛሬ ይፋ ያደረገው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ፥ ኢሕአዴግና አጋሮቹ ከ547 የፓርላማ መቀመጫዎች፥ 546ቱን ማሸነፋቸውን አመልክቷል። ውጤቱ እየተጠበቀ ያለው ብቸኛው የግል ፓርላማ አባል ዶክተር አሸብር ወልደጊዮርጊስ የተወዳደሩበት የቦንጋ ጊምቢ ቦጎአካ የምርጫ ክልል ነው።

ይህ በእንዲህ እንዳለ፤ “የምርጫው ውጤት ፈላጭ ቆራጭ አገዛዝን በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ ጭኜ መግዛት እችላለሁ የሚለውን መልእክት ኢሕአዴግ ያስተላለፈበት ነው፤” ሲሉ አንድ የመድረክ አመራር አባል ተናገሩ። የሰማያዊ ፓርቲ ፕሬዘዳንት በኩላቸው ውጤቱ አላስገረመኝም ብለዋል።

እስካሁን ይፋ በሆኑ የምርጫ ውጤቶች ያልተገለጸው አንድ መቀመጫ የግሉ ተወዳዳሪ ዶ/ር አሸብር ወልደጊዮርጊስ የተወዳደሩበት ቦንጋ ጊምቦ ጎአታ የምርጫ ክልል ጨምሮ በእለቱ አቢይ ርዕስ የተዳሰሱትን ዘገባዎች ዝርዝር ከዚህ ያድምጡ።

XS
SM
MD
LG