በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ኢትዮጵያ፣ ግብፅ፣ ዓባይ፣ ኅዳሴ


የትረምፕ አስተዳደር የኢትዮጵያን፣ የግብፅንና የሱዳንን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ለውይይት ወደ ዋሺንግተን ዲሲ ጋብዟል።

ዶ/ር ስለሺ በቀለ /ሚኒስትር/
ዶ/ር ስለሺ በቀለ /ሚኒስትር/

የትረምፕ አስተዳደር የኢትዮጵያን፣ የግብፅንና የሱዳንን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ለውይይት ወደ ዋሺንግተን ዲሲ ጋብዟል።

የጥሪው አጀንዳ የኅዳሴ ግድብ አሞላልና በዓባይ ውኃ አጠቃቀም ላይ በካይሮና በአዲስ አበባ መካከል አለ የሚባለው አለመግባባት መሆኑ ተገልጿል።

ታላቁ ኅዳሴ ግድብ /በከፊል/
ታላቁ ኅዳሴ ግድብ /በከፊል/

ስብሰባውን እንዲጠሩ ለፕሬዚዳንት ትረምፕ ጥሪ ያቀረቡት የግብፁ አብዱልፋታህ ኤል ሲሲ ናቸው።

ጉዳዩ በቴክኒክ ባለሙያዎች የተያዘ በመሆኑ ኢትዮጵያና ሱዳን የሦስተኛ ወገን አደራዳሪ በማስገባት ሃሳብ እንደማይስማሙ ለቪኦኤ በሰጡት ቃል የተናገሩት የኢትዮጵያ የውኃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶ/ር ስለሺ በቀለ ፕሬዚዳንት ትረምፕ የጋበዙት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮችን መሆኑንና የድርድርም አለመሆኑን ተናግረዋል።

ለሙሉው ቃለ ምልልስ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።

ኢትዮጵያ፣ ግብፅ፣ ዓባይ፣ ኅዳሴ
please wait

No media source currently available

0:00 0:30:28 0:00


የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG