በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

እሥር ላይ ባሉ የተቃዋሚ መሪዎች ላይ እሥራት ተወሰነ፤ ቀሪው ተቀጠረ


ፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት
ፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት

please wait

No media source currently available

0:00 0:03:02 0:00
ቀጥተኛ መገናኛ

የኢትዮጵያ ፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ችሎት በሽብር ተከስሰው እሥር ቤት ውስጥ በሚገኙ ሦስት የተቃዋሚ ፓርቲ አመራር አባላት ላይ ዛሬ ተጨማሪ የእሥራት ቅጣት ወስኗል፡፡

በነዘላለም ወርቅአገኘሁ ዶሴ ከተከሰሱት መካከል የአንድነት ፓርቲ አመራር አባል የነበሩት ዳንኤል ሺበሺ፤ የአረና ትግራይ አመራር አባል የነበሩት አብረሃ ደስታና የሰማያዊ ፓርቲ አመራር አባል የነበሩት የሺዋስ አሰፋ ችሎት በመድፈርና በማንጓጠጥ ከዋናው ክሥ ውጭ ነው የተወነጀሉት፡፡

አቃቤ ሕግ በሰባተኛው ተከሣሽ ላይ ያሻሻለውን ክሥ ፍርድ ቤቱ ተቀብሎታል፡፡

ተከሣሾቹ በተያዘው ቀጠሮ የእምነት ክሕደት ቃል ይሰጣሉ ተብሏል፡፡

XS
SM
MD
LG