በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

አራት ሚሊየን ዓመት የሚጠጋ ዕድሜ ያለው የሰው መሰልና የጦጣ መሰል ድብልቅ


ኢትዮጵያ ውስጥ የተገኘው ወደ አራት ሚሊየን ዓመት የሚጠጋ ዕድሜ ያለው የሰው መሰልና የጦጣ መሰል ድብልቅ የሆኑ መገለጫዎች ይሉት ቅሪተ-አካል የዛሬ አርባ አምስት ዓመት አፋር ውስጥ የተገኘችው የሉሲ ወይም አውስትራሎፔቲከስ አፋሬንሲስ ቀጥተኛ ቅድመ-ትውልድ ሊሆን እንደሚችል ተገልጿል።

ይህ የ3.8 ሚሊየን ዓመት ዕድሜ ያለው ቅሪተ-አካል የ4.2 ሚሊየን ዓመት ዕድሜ ያስቆጠረውንና ከሰው ዝርያ ጋር ግንኙነት አለው የሚባለውን የቀደመውን አውስትራሎፒቴከስ አናሜንሲስ በተሻለ ሁኔታ ለማጥናትና ለመረዳት ዕድል የሚከፍት መሆኑ በሳይቲስቶቹ ተነግሯል።

አጥኚዎቹ የቅሪተ-አካል ባለሙያዎች ኤም.አር.ዲ. ብለው የጠሩት የአሁኑ ግኝት የወጣው ቀድሞ የሉሲ አፅሞች ከተገኙበት የአፋር አካባቢ ሃምሣ አምስት ኪሎሜትር ርቀት ላይ የተገኘው የዛሬ ሦስት ዓመት አካባቢ መሆኑ ተገልጿል።

ሉሲና ኤም.አር.ዲ. የሰው ልጅ አመጣጥን ለመተርተር ለሚደረገው ጥረት የጎላ ብርሃን እንደሚሰጡ ተነግሯል።

ጥናቱ የተመራው የክሊቭላንዱ የተፈጥሮ ታሪክ ቤተ-መዘክር ባልደረባ በሆኑት ቅሪተ-አካል ተመራማሪ ዮሃንስ ኃይለሥላሴ ነው።

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG