ዋሽንግተን ዲሲ —
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን በዓለምአቀፉ የብሔራዊ ሰብዓዊ መብቶች ተቋማት ኅብረት የአንደኛ ደረጃ ዕውቅና እንደተሰጠው አስታወቀ። ዕውቅናው በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የተለያዩ ተቋሞች ውስጥ ነፃና ቀጥተኛ ተሳትፎ ሊያደርግ እንደሚያስችለውም ተገልጿል።
ኅብረቱ በተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ መብቶች ከፍተኛ ኮሚሽነር ቢሮና በአውሮፓ ኅብረት በጋራ የሚታገዝ ተቋም ነው።