ዋሺንግተን ዲ.ሲ.- አዲስ አበባ —
አባይ ወንዝ ላይ እየተገነባ ባለው የኅዳሴ ግድብ ዙሪያ በግብፅ እና በኢትዮጵያ መካከል በተፈጠረው ውዝግብ ላይ ለመነጋገር በግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሞሐመድ ካመል አምር የተመራ ከፍተኛ የልዑካን ቡድን ዛሬ አዲስ አበባ ገብቷል፡፡
የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃልአቀባይ አምባሣደር ዲና ሙፍቲ ማምሻውን ለቪኦኤ በሰጡት መግለጫ የልዑካን ቡድኑ ከኢትዮጵያ አቻው ጋር ነገ ሰኞ፣ ሰኔ 10/2005 ዓ.ም ጠዋት ለውይይት እንደሚቀመጥ ታውቋል፡፡
ለጊዜው ቁጥሩን ባይጠቅሱም የግብፁ ቡድን በርካታ አባላት ያሉት መሆኑን አምባሣደር ዲና አመልክተው ቡድኑ ወደ ኢትዮጵያ የተጓዘው በራሷ በግብፅ ጥያቄ እንደሆነ ገልፀዋል፡፡
ሰሞኑን የግብፅ ባለሥልጣናት በግድቡ ግንባታ ላይ እያሰሙ ያሉትን ነቀፌታና ፕሬዚዳንት ሞሐመድ ሞርሲ ለሕዝባቸው በቴሌቪዥን ባደረጉት ንግግር ያስተላለፉትን ዛቻና ማስፈራሪያ መሰል መልዕክት አስመልክቶ ማብራሪያ ለመጠየቅ የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አዲስ አበባ የሚገኙትን የግብፅ አምባሣደር ሁለት ጊዜ ጠርቶ ማነጋገሩንም አምባሣደር ዲና አመልክተዋል፡፡
የሰኞው ውይይት ይጠናቀቃል የተባለው ነገ ረፋድ ላይ በሚደረገው ውይይት ሲሆን ማራዘም አስፈላጊ ሆኖ ካልተገኘ በስተቀር የቡድኑ ጉብኝት የተያዘው ለአንድ ቀን ብቻ መሆኑን የውጭ ጉዳዩ ቃልአቀባይ ገልፀዋል፡፡
ዘገባውን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡
የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃልአቀባይ አምባሣደር ዲና ሙፍቲ ማምሻውን ለቪኦኤ በሰጡት መግለጫ የልዑካን ቡድኑ ከኢትዮጵያ አቻው ጋር ነገ ሰኞ፣ ሰኔ 10/2005 ዓ.ም ጠዋት ለውይይት እንደሚቀመጥ ታውቋል፡፡
ለጊዜው ቁጥሩን ባይጠቅሱም የግብፁ ቡድን በርካታ አባላት ያሉት መሆኑን አምባሣደር ዲና አመልክተው ቡድኑ ወደ ኢትዮጵያ የተጓዘው በራሷ በግብፅ ጥያቄ እንደሆነ ገልፀዋል፡፡
ሰሞኑን የግብፅ ባለሥልጣናት በግድቡ ግንባታ ላይ እያሰሙ ያሉትን ነቀፌታና ፕሬዚዳንት ሞሐመድ ሞርሲ ለሕዝባቸው በቴሌቪዥን ባደረጉት ንግግር ያስተላለፉትን ዛቻና ማስፈራሪያ መሰል መልዕክት አስመልክቶ ማብራሪያ ለመጠየቅ የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አዲስ አበባ የሚገኙትን የግብፅ አምባሣደር ሁለት ጊዜ ጠርቶ ማነጋገሩንም አምባሣደር ዲና አመልክተዋል፡፡
የሰኞው ውይይት ይጠናቀቃል የተባለው ነገ ረፋድ ላይ በሚደረገው ውይይት ሲሆን ማራዘም አስፈላጊ ሆኖ ካልተገኘ በስተቀር የቡድኑ ጉብኝት የተያዘው ለአንድ ቀን ብቻ መሆኑን የውጭ ጉዳዩ ቃልአቀባይ ገልፀዋል፡፡
ዘገባውን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡