በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የኢዜማ መግለጫ እና የህወሓት ምላሽ


የኢዜማ መግለጫ እና የህወሓት ምላሽ
please wait

No media source currently available

0:00 0:03:08 0:00

“ህወሓት ትጥቅ ባለመፍታቱ በጠብ አጫሪነቱ ቀጥሏል፤” ሲል የከሰሰው የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ/ኢዜማ/ ፓርቲ፣ ባለፈው ሳምንት ማብቂያ ላወጣው መግለጫ፣ ህሓት ምላሽ ሰጠ።

ኢዜማ፣ ባለፈው ሳምንት በራያ አላማጣ ወረዳ አካባቢ የተፈጠረውን ክሥተት በተመለከተ፣ ህወሓትን ወቅሶ ባወጣው መግለጫ፣ የፌደራሉ መንግሥት ትጥቁን በማስፈታት ሕግንና ሥርዓትን እንዲያስከብር ጠይቋል።

በጉዳዩ ላይ ለአሜሪካ ድምፅ ጥያቄ ምላሽ የሰጡት፣ በህወሓት ጽሕፈት ቤት የፕሮፓጋንዳ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ኢያሱ ተስፋይ፣ ድርጅታቸው በፈረመው የፕሪቶርያው ስምምነት መሠረት በሰላማዊ መንገድ እንደሚንቀሳቀስ ገልጸዋል፡፡ በአንጻሩ ኢዜማ ክሱን ያቀረበው፣ በስምምነቱ መሠረት እየተፈጸመ ነው ያሉትን ሰላማዊ እንቅስቃሴ ስለማይፈልግ ነው፤ ብለዋል፡፡

ዝርዝር ዘገባውን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

XS
SM
MD
LG