ስብሰባውን ያዘጋጀው ከሰባ በላይ በሚሆኑ ሃገሮች ውስጥ የሚንቀሣቀሰው ዓለምአቀፍ የግብርናና የገጠር ልማት ትብብር ድርጅት ነው፡፡
ዋና ፅሕፈት ቤታቸው ሆላንድ የሆነውን የድርጅቱን ዋና ዳይሬክተርና ስብሰባውን የጠሩትን አቶ ሚካኤል ኃይሉን ሰሎሞን አባተ አነጋግሯቸው ስለድርጅታቸውና ስለስብሰባው ምንነት አስረድተዋል፡፡
በአፍሪካ ቀንድ አካባቢ እንኳን ሰፊ የገበያ ፍላጎት እንዳለ አቶ ሚካኤል ጠቁመው ድርጅታቸውም የየሃገሩን ገበሬ የማቅረብ አቅም የእሴት ሠንሰለቱን በማጠናከር ለማጎልበት እንደሚሠራ አመልክተዋል፡፡
ከሰባ በላይ ከሚሆኑ የአፍሪካ የፓሲፊክ እና የካሪቢያን ሃገሮች የተሰበሰቡት ከአምስት በላይ የአዲስ አበባው ጉባዔ ተሣታፊዎች የልምድ ልውውጥ ማድረጋቸውንና የተለያዩ ግብርናና ገበያ ነክ ፕሮጀክቶችን መጎብኘታቸውን አቶ ሚካኤል ገልፀዋል፡፡
ቃለ ምልልሱን ያዳምጡ