No media source currently available
በኢትዮጵያ የኮቪድ ወረርሽኝ ሦስተኛው ማዕበል እየጀመረ መሆኑን የሚጠቁሙ ምልክቶች እየታዩ ናቸው ሲል የኢትዮጵያ የኅብረተሰብ ጤና ኢንስትቲዩት አስታወቀ። ዴልታ የተሰኘው አዲሱ የኮቪድ-19 ዝርያ በሃገሪቱ መኖር አለመኖሩን በቅርቡ እንደሚያረጋግጥም ገለፀ። ወደ 22 ለሚሆኑ ኢትዮጵያውያን በስድስት ወር ውስጥ የኮቪድ ክትባትን ለማዳረስም እየተሠራ ነው ተባለ።