በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የሕገ መንግሥት አጣሪው ሥራውን አጠናቀቀ


የሕገ መንግሥት ጉዳዮች አጣሪ ጉባኤ በሦስት ዙር ያካሄደውን ይፋ የሙያ ምስክርነት የመስማት ሂደት ዛሬ አጠናቋል።

የጉባኤው ሰብሰቢ የሆኑት የጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት መዓዛ አሸናፊ እንዳሉት ከቀረቡት 22 የፅሁፍ አስተያየቶች አብዛኛዎቹ ወደ ተመሳሳይ ድምዳሜ የሚያመለክቱ ናቸው።

ዛሬ ምስክርነታቸውን የሰጡ የጤና ሚኒስቴር እና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባለሥልጣናት እና የሥራ ኃላፊዎችም ባለው የኮሮና ወረርሽኝ እና በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ውስጥ ምርጫ ማካሄድ እንደማይቻል አብራርተዋል።

ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።

የሕገ መንግሥት አጣሪው ሥራውን አጠናቀቀ
please wait

No media source currently available

0:00 0:07:16 0:00


XS
SM
MD
LG