በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የቻይና ኢኮኖሚ


ጠቅላይ ሚኒስትር ሊ ኪኪያንግ
ጠቅላይ ሚኒስትር ሊ ኪኪያንግ

በምጣኔ ሃብት ከዓለም ሁለተኛዋ ቻይና - ዘንድሮ ከገጠማት አነስተኛ እድገትና ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር የንግድ ንትርክ ውስጥ በመሆኗ ከባድ ፈተና ይጠብቃታል ሲሉ የሃገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ሊ ኪኪያንግ አስጠነቀቁ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ 3000 ሺህ ልዑካን ለተገኙበት ብሄራዊው የሕዝብ ምክር ቤት ባደረጉት ዓመታዊ ንግግር ቤይጂንግ በዚህ ዓመት የምትጠብቀው የኢኮኖሚ እድገት - ከ 6 እስከ 6 ነጥብ 5 በመቶ ይሆናል ሲሉ አስረድተዋል። ብዙ ሃገሮች ይህን የእድገት መጠን ለማስመዝገብ የሚቸገሩ ሲሆን፡ ለቻይና ግን ከ 30 ዓመታት ወዲህ ዝቅተኛው እንደሚሆን ተገምቷል።

የቻይና ኮሚኒስት አመራር ሀገሪቱን ከዚህ ከባድ የኢኮኖሚ ማዕበል ሊያወጣ እንደሚችል እምነታቸው መሆኑን ግን ጠቅላይ ሚኒስትር ሊ ኪኪያንግ አስታውቀዋል።

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG