በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የቻይናው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አስመራ ገቡ


የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ዪ እና ኤርትራ ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ
የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ዪ እና ኤርትራ ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ

በቻይናው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ዪ የተመራ የልኡካን ቡድን ኤርትራን ለመጎብኘት በዛሬው ዕለት አስመራ መግባቱና ከፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂም ጋር ተገናኝቶ መነጋገሩ ተነገረ፡፡

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ዋንግ ዪ ከቻይናው መሪ ፕሬዚዳንት ዢ ጂፒንግ የተላከ መልዕክት ለኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ማድረሳቸው የተመለከተ ሲሆን ቻይናና ኤርትራ የጋራ ግንኙነታቸውን ለማጠንከር መስማምታቸው ተገልጿል፡፡

የኤርትራው መሪ ቻይናን እንዲጎበኙ ከቻይናው ፕሬዚዳንት ጥሪ የተደረገላቸው መሆኑም ከስፍራው በደረሰን ዘገባ ተመልክቷል፡፡

XS
SM
MD
LG