ዋሽንግተን ዲሲ —
በቻይናው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ዪ የተመራ የልኡካን ቡድን ኤርትራን ለመጎብኘት በዛሬው ዕለት አስመራ መግባቱና ከፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂም ጋር ተገናኝቶ መነጋገሩ ተነገረ፡፡
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ዋንግ ዪ ከቻይናው መሪ ፕሬዚዳንት ዢ ጂፒንግ የተላከ መልዕክት ለኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ማድረሳቸው የተመለከተ ሲሆን ቻይናና ኤርትራ የጋራ ግንኙነታቸውን ለማጠንከር መስማምታቸው ተገልጿል፡፡
የኤርትራው መሪ ቻይናን እንዲጎበኙ ከቻይናው ፕሬዚዳንት ጥሪ የተደረገላቸው መሆኑም ከስፍራው በደረሰን ዘገባ ተመልክቷል፡፡