በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የካሜሩን የጦር ሠራዊት 300 የቦኮ ሐራም ታጋቾችን አስለቀቀ


የካሜሩን የጦር ሠራዊት 300 የቦኮ ሐራም ታጋቾችን አስለቀቀ
please wait

No media source currently available

0:00 0:03:09 0:00

የካሜሩን የጦር ሠራዊት 300 የቦኮ ሐራም ታጋቾችን አስለቀቀ

የካሜሩን የጦር ኃይል በናይጄሪያው ሽብርተኛ ቡድን በቦኮ ሐራም ቁጥጥር ሥር የነበሩ ከ300 በላይ ታጋቾች አስለቅቋል።

የጦር ኃይሉ ካሜሩንን ከናይጄሪያ እና ከቻድ ጋር በሚያዋስናት የድንበር አካባቢ "አልፋ" በሚል ስያሜ ባካሄደው አንድ ሳምንት የፈጀ ዘመቻ ብዛት ያላቸው የናይጄሪያው ቦኮ ሐራም ታጣቂዎችን መግደሉን አስታውቋል።

ያስለቀቃቸውን ታጋቾች በሰሜናዊ የሀገሪቱ ክፍል ወደሚገኝ የጦር ሠፈር ወስዶ ማስፈሩንም አመልክቷል። ሞኪ ኤድዊን ኪንድዜጋ ከያውንዴ ያስተላለፈው ዘገባ ዝርዝሩን ይዟል።

ቆንጅት ታየ ወደ አማርኛ መልሳዋለች።

መድረክ / ፎረም

XS
SM
MD
LG