በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

“እስራኤል እና ፍልስጤም በሰላም የሚኖሩበት መፍትሄ ግድ ነው” ብሊንከን


“እስራኤል እና ፍልስጤም በሰላም የሚኖሩበት መፍትሄ ግድ ነው” ብሊንከን
please wait

No media source currently available

0:00 0:02:58 0:00

የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ከትላንት በስቲያ እሁድ እና ትላንት ሰኞ ግብፅን እና እስራኤልን በጎበኙበት ወቅት ዩናይትድ ስቴትስ ለመካከለኛው ምስራቅ ሰላም ያላትን ቁርጠኝነት አረጋግጠዋል።

ይህ ገለጻቸው የተሰማው በአካባቢው የሚታየው ብጥብጥ በቀጠለበት እና ኢራን የኒውክሌር ጦር መሳሪያ ለመሆን የያዘችውን ጥረት አስመልክቶ ያለው ስጋት እየጨመረ በመጣበት ወቅት ነው።

ይህ በእንዲህ እንዳለ: ብሊንከን በዛሬው ዕለት ወደ ዌስት ባንክ ከማምራታቸው አስቀድሞ በእስራኤል እና በአረብ ሃገሮች መካከል ሰላማዊ ግንኙነት ለመፍጠር ስለተደረጉት ስምምነቶች አስፈላጊነት አጽንኦት በሰጡበት አስተያየት፤ ሁለቱን አገሮች .. እስራኤልን እና ፍልስጤምን በሰላም ለመኖር የሚያስችል መፍትሄ ስለሚያማጣ እድልም ተናግረዋል።

XS
SM
MD
LG