በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የሆራ ሀርሴዴ የኢሬቻ በዓል በቢሾፍቱ ተከበረ


የሆራ ሀርሴዴ የኢሬቻ በዓል በቢሾፍቱ ተከበረ
please wait

No media source currently available

0:00 0:03:28 0:00

የሆራ ሀርሴዴ የኢሬቻ በዓል በቢሾፍቱ ተከበረ

የኦሮሞ ሕዝብ የምስጋና ጊዜ የሆነው የሆራ ሀርሰዴ የኢሬቻ በዓል ዛሬ መስከረም 26 ቀን 2017 ዓ/ም በቢሾፍቱ ከተማ ተከብሯል።

“ሆራ ሀርሴዴ ልዩ ክብር ያለውና የኦሮሞ ሕዝብ መስዋዕት የከፈለበት ቦታ ነው” ሲሉ የአሜሪካ ድምፅ ያነጋገራቸው ተሳታፊዎች ገልፀዋል።

በሚሊዮን የሚቆጠር ህዝብና አባገዳዎች፣ ሀደ ሲንቄዎች፣ ከተለያዩ የአገሪቱ አካባቢዎች እና ከጎረቤት ሀገራት የመጡ እንግዶች እንዲሁም የውጭ ሀገራት ቱሪስቶች በበዓሉ መታደማቸውን የገለጸው ደግሞ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ነው።

ኮሚሽኑ ዛሬ ባወጣው መግለጫ “የሆራ ሀርሰዴ የኢሬቻ በዓል ያለ ምንም የፀጥታ ችግር በሰላም ተጠናቋል” ሲል አስታውቋል።

መድረክ / ፎረም

XS
SM
MD
LG