በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል የኦነግን ባንዲራ በያዙ ታጣቂዎች ጥቃት እንደተከፈተበት አስታወቀ


በማኅበራዊ ሚዲያ ፌስቡክና ትዊተር ላይ አግኝተን በስክሪን ኮፒ የወሰድነው ፎቶ ግራፍ ነው።
በማኅበራዊ ሚዲያ ፌስቡክና ትዊተር ላይ አግኝተን በስክሪን ኮፒ የወሰድነው ፎቶ ግራፍ ነው።

የኦሮሞ ነፃ አውጪ ግንባር (ኦነግ) በበኩሉ ሠራዊቱ በእንደዚህ ዓይነት ተግባር ላይ እንደማይሰማራ አስታውቋል።

በቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል አራት የካማሽ ዞን አመራሮች በታጣቂዎች መገደል የቀሰቀሰው ግጭት ለብዙ ሺዎች መፈናቀል ምንክኒያት ሆኗል ተብሏል።

የክልሉ መንግሥት በበኩሉ ከሰኔ 16/2010 ጀምሮ የተለያዩ ግጭቶች እየተፈጠሩ መሆኑን ገልፆ የአመራሮቹ በታጣቂዎች መገደል ደግሞ ነገሩን የበለጠ እንዳባባሰው ጠቁመዋል።

በአሁኑ ሰዓትም የፌደራልና የመከላከያ ሰራዊ አባላት ግጭቶቹ ወደ ተፈጠሩባቸው አምስት ወረዳዎች ገብተው በማረጋጋት ላይ እንደሆኑም ገልፀዋል።

ጥቃቱ በአምስት ወረዳዎች መድረሱን የሚናገሩት ነዋሪዎች በበኩላቸው ከአንዳንዶቹ ወረዳዎች ቀያቸውን ጥለው በመሰደድ ላይ እንደሚገኙ ሲናገሩ በአንዳንዶቹ ደግሞ ባሉበት አንድ ላይ መጠለያ ውስጥ ተሸሽገው እንደሚገኙ ተናግረዋል።

ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያድምጡ።

የቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል የኦነግን ባንዲራ በያዙ ታጣቂዎች ጥቃት እንደተከፈተበት አስታወቀ
please wait

No media source currently available

0:00 0:16:16 0:00

በካማሽ ጉዳይ የአርብ ምሽት ዘገባ

please wait

No media source currently available

0:00 0:07:38 0:00

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG