በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በባሕር ዳር ሰባታሚት አካባቢ ግጭት የጥበበ ግዮን ልዩ ሆስፒታል አገልግሎት እንዳቆመ ተገለጸ


በባሕር ዳር ሰባታሚት አካባቢ ግጭት የጥበበ ግዮን ልዩ ሆስፒታል አገልግሎት እንዳቆመ ተገለጸ
please wait

No media source currently available

0:00 0:08:06 0:00

በባሕር ዳር ሰባታሚት አካባቢ ግጭት የጥበበ ግዮን ልዩ ሆስፒታል አገልግሎት እንዳቆመ ተገለጸ

ከባሕር ዳር ከተማ በቅርብ ርቀት ላይ የሚገኘውና በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የሕክምና እና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ሥር የሚገኘው የጥበበ ግዮን ልዩ ሆስፒታል፣ መደበኛ አገልግሎት መስጠት እንዳቆመ፣ የሆስፒታሉ ሐኪሞች እና ሠራተኞች ገለጹ።

ለአሜሪካ ድምፅ አስተያየታቸውን የሰጡና ስማቸውን መጥቀስ ያልፈለጉ የጤና ባለሞያዎች ለአሜሪካ ድምፅ እንደገለጹት፣ ሆስፒታሉ አገልግሎት መስጠት ያቋረጠው፣ በቅርቡ በመንግሥት የጸጥታ ኀይሎች እና በፋኖ ቡድን ታጣቂዎች መካከል፣ ባለፈው ሳምንት ማክሰኞ፣ በአቅራቢያው የተፈጠረውን ግጭት ተከትሎ ነው፡፡ በግጭቱ ለደኅንነታቸው የሰጉ የሕክምና ባለሞያዎች፣ ሆስፒታሉን እየለቀቁ ወጥተዋል፤ ብለዋል የጤና ባለሞያዎቹ፡፡

ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ ሁለት የዩኒቨርሲቲው ባለሥልጣናት፣ የሆስፒታሉ ሠራተኞች፣ ከትላንት እሑድ ጀምሮ፣ በከፊል በሥራ ገበታቸው ላይ እንደማይገኙ ተናግረዋል፡፡

በአሜሪካ ድምፅ ዘጋቢዎች የተጠናቀረ ዘገባ ነው፡፡

መድረክ / ፎረም

XS
SM
MD
LG