በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በአውስትራልያ ለተከሰተው የሰደድ እሳት ሰለባ ለሆኑ እርዳታ


የአውስትራልያ ጠቅላይ ሚኒስትር ስካት ሞሪሰን
የአውስትራልያ ጠቅላይ ሚኒስትር ስካት ሞሪሰን

የአውስትራልያ ጠቅላይ ሚኒስትር ስካት ሞሪሰን በሀገሪቱ የተከሰተው አስከፊ የሰደድ እሳት ሰለባ የሆኑትን ሰዎች ለመርዳት “አስፋላጊውን ሁሉ” ለመክፈል ቃል ገብተዋል።

የሰደድ እሳቱ በሦስት ክፍላተ ሀገር በሚሊዮኖች የሚቆጠር ሄክታር ቦታዎችን አጋይቷል።

ሞሪሰን ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ የወደሙትን ከተሞችና መሰረተ ልማቶችን መልሶ ለመገንባት ተጨማሪ አንድ ነጥብ አራት ቢልዮን ዶላር መመደባቸውን ገልጸዋል። እንደ አስፈላጊነቱም ተጨማሪ ገንዘብ እንደሚመደብ መንግሥታቸው አስታውቋል።

ከተመደበው በላይ ካስፈለገም ይጨመራል ብለዋል ሞሪሰን።

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG