ነብያት ጥጋቡ በደቡብ አፍሪካ የሚኖር ኢትዮጵያዊ ስደተኛ ነው።
ትምህርቱን ሊያጠናቅቅ ሲል ከጓደኞቹ ጋር በመሆን የመላው አማራ አንድነት ድርጅትን ለመቀላቀል እንደወሰነ ይናገራል። ነገር ግን ይሄ ውሳኔው ችግር ውስጥ እንደጣለውና ለሕይወቱ በመስጋቱም አገር ጥሎ ወደ ደቡብ አፍሪካ ለመሰደድ እንደተገደደ ነብያት ተናግሯል።
ዘጋቢያችን ኒኮ ፒኖ ነብያት ጥጋቡን ስለ ኑሮው አነጋግሮታል። ቃለ-መጠይቁን ያዳምጡ።