የኢህአዲግ 8ኛው ድርጅታዊ ጉባኤ መስከረም 3 ቀን 2003 ዓ ም በናዝሬት ከተማ ተካሂዷል፡፡ በጉባኤው መክፈቻ ላይም ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ንግግር አሰምተዋል፡፡ የቻይና የህንድና የተለያዩ አገሮች ተወካዮችም እንግድነት ተገኝተዋል፡፡ አትሌት ሻለቃ ሀይሌ ገብረስላሴ በቦታው በመገኘት፤ ለጊዜ ከፍተኛ ግምት ሊሰጥ እንደሚገባ አስታውሷል፡፡ ጉባኤውም በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን በቀጥታ ተላልፏል፡፡ ዝርዝሩን በቦታው ተገኝቶ ካጠናከረው ዘገባ ያድምጡ፡፡