ከአብን ሰልፍ ጋር በተያያዘ በእስር የነበሩ ሰዎች እየተለቀቁ ነው
ለረቡዕ ጥቅምት 18/2013 ዓ.ም ጠርቶ ከነበረው የተቃውሞ ሰልፍ ጋር በተያያዘ የታሰሩ ግለሰቦች እንዳሉ ያረጋገጡት የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽነር አበረ አዳሙ አሁን ግን እየተለቀቁ ነው ብለዋል። ሰልፍ በተጠራበት ቀን እንወጣለን ያሉ ጥቂት ወጣቶች ከፖሊስ ጋር ተጋጭተው ታስረው ነበር ነው ያሉት። ሰልፉን የጠራው የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ /አብን/ የታሱሩ አባላቱ እየተፈቱ መሆኑን ጠቅሷል የተያዙት ግን በቢሮ ውስጥ እንዳሉ እንጅ ሰልፍ ወጥተው አይደለም ብሏል።
የፕሮግራሙ ተከታታይ ክፍሎች
-
ፌብሩወሪ 17, 2025
ብርቅዬው ዋልያ አይቤክስ የህልውና አደጋ ውስጥ እንደሚገኝ ባለሥልጣኑ አስታወቀ
-
ፌብሩወሪ 14, 2025
በሰሜን ጎጃም ጎንጂ ቆለላ ወረዳ 13 መምህራን በታጣቂዎች ታግተው መወሰዳቸውን ቤተሰቦች ተናገሩ
-
ፌብሩወሪ 14, 2025
የፕሬዝዳንት ትራምፕ የውጭ ግንኙነት ፖሊሲ ርምጃዎች እና ሉላዊ ተጽእኗቸው
-
ፌብሩወሪ 14, 2025
በሲዳማ ከአንድ ቤት ሦስት ህፃናት በቃጠሎ ሞቱ