በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በጅጋ ከተማ በቀጠለ ግጭት ሲቪሎች መገደላቸውን ነዋሪዎች ገለጹ


የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር መዲና ባህር ዳር ከተማ
የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር መዲና ባህር ዳር ከተማ

በምዕራብ ጎጃም ዞን ጃቢጠህናን ወረዳ ጅጋ ከተማ፣ ከትላንት በስቲያ እሑድ፣ በመንግሥት እና በፋኖ ቡድን ታጣቂዎች መካከል የተነሣውን ግጭት ተከትሎ፣ ሲቪሎች መገደላቸውን ነዋሪዎች ገለጹ።

ጅጋን ከተማና የአካባቢው ሕዝብ በመወከል የተመረጡት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል በበኩላቸው ሲቪሎች መገደላቸውን ገልጸው፤ ጉዳዩን ለአገር ውስጥ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ማሳወቃቸውን ተናግረዋል።

በጅጋ ከተማ በቀጠለ ግጭት ሲቪሎች መገደላቸውን ነዋሪዎች ገለጹ
please wait

No media source currently available

0:00 0:06:51 0:00

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን የባሕር ዳር ቅርንጫፍ፣ ጉዳዩን በማጣራት ላይ እንደሚገኝ ገልጿል። ከክልሉ እና ከፌደራል መንግሥት ባለሥልጣናት መረጃ ለማግኘት ያደረግነው ጥረት አልተሳካም።

አስቴር ምስጋናው የአካባቢውን ነዋሪዎች እና የሰብአዊ መብት ኮሚሽን አስተያየት ጠይቃ ያጠናቀረችውን ዘገባ እንደሚከተለው ታቀርበዋለች።

መድረክ / ፎረም

XS
SM
MD
LG