በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

መንግሥት በድንበር ተሻጋሪ አሽከርካሪዎች ላይ የተባባሰውን የታጣቂዎች ጥቃት አለመግታቱ ተገለጸ


መንግሥት በድንበር ተሻጋሪ አሽከርካሪዎች ላይ የተባባሰውን የታጣቂዎች ጥቃት አለመግታቱ ተገለጸ
please wait

No media source currently available

0:00 0:07:22 0:00

በኢትዮ-ጅቡቲ መሥመር የሚመላለሱ የከባድ መኪና አሽከርካሪዎች፣ በታጣቂዎች ይደርስብናል ያሉት ጥቃት እየተባባሰ መምጣቱን ለአሜሪካ ድምፅ አስታወቁ፡፡

አሽከርካሪዎችን አፍኖ በክፍያ ከመደራደር ጀምሮ፣ ተኩስ ከፍቶ እስከ መግደል እና የአካል ጉዳት እስከ ማድረስ የሚዘልቅ ተደጋጋሚ ችግር እየተስተዋለ መኾኑን፣ አሽከርካሪዎቹ ገልጸዋል፡፡

የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር፣ ለደኅንነት ስጋታቸው በአጭር ጊዜ ውስጥ እልባት እንደሚሰጥ ቃል ቢገባም፣ ከዕለት ወደ ዕለት የሚፈጸምባቸው ጥቃት ተባብሶ መቀጠሉን አሽከርካሪዎቹ ያመለክታሉ፡፡

በአገሪቱ ልዩ ልዩ አካባቢዎች የሚስተዋለውን የጸጥታ መደፍረስ ተከትሎ፣ በአሽከርካሪዎች ላይም ጥቃቶች መበራከታቸውን ያረጋገጠው የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን፣ ጉዳዩ እንደሚያሳስበው ገልጿል፡፡

የአሜሪካ ድምፅ ያነጋገራቸው የከባድ መኪና አሽከርካሪዎች፣ ባለፉት አንድ ወር ከዐሥራ አምስት ቀናት ውስጥ፣ እነርሱ የሚያውቋቸው አምስት አሽከርካሪዎች እና ረዳቶቻቸው፣ ማንነታቸው በአልታወቁ ታጣቂዎች ከታፈኑ በኋላ መገደላቸውን ተናግረዋል፡፡

በጅቡቲ መሥመር ለ20 ዓመታት በከባድ መኪና አሽከርካሪነት እንደሠሩ የሚናገሩት እና ለደኅንነቴ ሲባል ስሜም አይጠቀስ ድምፄም ይቀየር ያሉ አስተያየት ሰጪ፣ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ መሥመሩ፣ ለአሽከርካሪዎችም ኾነ ለተሳፋሪዎች የስጋት ምንጭ እንደኾነ ገልጸዋል፡፡

XS
SM
MD
LG