በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ማድሊን ኦልብራይት የመጨረሻ ስንብት ተደረገላቸው

የዓለም መሪዎችና የዩናይትድ ስቴትስ ዕውቅ የፖለቲካና የውጭ ፖሊሲ ሰዎች ትናንት ረቡዕ በልጅነታቸው በጦርነት ከታመሰችው አውሮፓ በስደት መጥተው በዩናይትድ ስቴትስ የመጀመሪያዋ ሴት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ለመሆን የበቁትን የቀድሞዋን ዕውቅ ዲፕሎማት ማድሊን ኦልብራይትን የመጨረሻ ስንብት አድርገውላቸዋል፡፡

ስንብቱን የመሩት ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን፣ የቀድሞው ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማና እንዲሁም ኦልብራይትን ከፍተኛ ዲፕሎማታቸው አድርገው በመሾም በወቅቱ ዩናይትድ ስቴትስ ውስጥ ካሉት ሴቶች ሁሉ የላቀውን ሥልጣን እንዲኖራቸው ያስቻሏቸው የቀድሞው ፕሬዚዳንት ቢል ክሊንተን ነበሩ፡፡

በዋሽንግተን ብሄራዊ ካቴድራል የኦልብራይትን ህይወትና አበርክቶ ለመዘከር በተካሄደው የስንብት ሥነ ሥርዓት ላይ ወደ 1ሺ400 የሚጠጉ እንግዶች ተገኝተዋል፡፡


ተጨማሪ ይጫኑ

XS
SM
MD
LG