በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በአፍጋኒስታን መንገድ ላይ የተቀበረ ፈንጅ ፍንድቶ ከሠላሳ በላይ ሰዎች ሞቱ


የምዕራብ አፍጋኒስታን የጸጥታ ባለሥልጣናት እንደተናገሩት ሄራት እና ካንዳሃር የሚባሉትን ከተሞች በሚያገናኘው አውራ ጎዳና ላይ ሲያልፍ የነበረ አውቶቡስ፣ መንገድ ዳር በተቀበረ ፈንጂ ተመትቶ ሠላሳ አራት ሰዎች ተገደሉ፤ ሌሎች ወደአስራ ሰባት የሚሆኑ ደግሞ ቆስለዋል፡፡

ከአውቶቡስ ተሳፋሪዎች መካከል የሚበዙት ሴቶች እና ህፃናት እንደነበሩ አንድ የክፍለ ሀገሩ ባለሥልጣን አስታውቀዋል፡፡ ለጥቃቱ ኃላፊ ነኝ ያለ እስካሁን ባይኖርም በአካባቢው የሚንቀሳቀሱ የታሊባን ታጣቂዎች አዘውትረው የመንግሥት ባለሥልጣናትን እና የፀጥታ ኃይሎችን ዒላማ ያደረጉ ቦምቦችን መንገድ ዳር ይቀብራሉ።

ጥቃቶቹ እየተፈፀሙ ያሉት የዩናይትድ ስቴትስ ባለልስጣናት እና የታሊባን ተወካዮች ያሳተፈው የሰላም ድርድር ሊቀጠል በታቀደበት በአሁኑ ወቅት ነው።

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG