የኢትዮጵያ ፕሬዚዳንት ሣኅለ ወርቅ ዘውዴ ከአራት ዓመታት በኋላ በአድዋ ከተማ ላይ በተከበረው 128 ዓመት የዓድዋ በመታሰቢያ በዓል ላይ "አንድነታችን እናድስ ከታሪካችን ጋራ እንታረቅ" ሲሉ ጥሪ አቀረቡ። አባቶች ታሪክ በሠሩበት ተራርሮች ላይ ልጆቻቸው የእርስ በእርስ መገዳደል ታሪክ እንዳኖሩበት በቁጭት የተናገሩት ፕሬዚዳንቷ፣ በአሁኑ ጊዜም በአማራ ክልል የአንድ አገር ልጆች “እርስ በእስር እየተገዳደሉ ናቸው” ሲሉ ለሰላም ቅድሚያ እንዲሰጥ ጥሪ አቅርበዋል። በኦሮሚያ ክልልም “መሞት የሌላበች ንፁሃን እየሞቱ ነው” ብለዋል። የግጭቶች መቋጫ ውይይት እና ድርድር መኾኑን አስታውሰው ከእልቂት በፊት ችግሮች አስቀድሞ መፈታት እንደሚኖርባቸው ተናግረዋል። ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።
ኢትዮጵያውያን አንድነታቸውን እንዲያድሱ ፕሬዚዳንት ሣኅለወርቅ ጠየቁ
የፕሮግራሙ ተከታታይ ክፍሎች
-
ማርች 07, 2025
የክዋኔ ጥበብ እና የአካል ጉዳተኞች ተሳትፎ
-
ማርች 07, 2025
ጥንቃቄ የሚሻው የወጣቶች የማኅበራዊ ሚድያ አጠቃቀም
-
ማርች 06, 2025
ታሪፍ በአነስተኛ አምራቾች ላይ ያደረሰው ጉዳት
-
ማርች 06, 2025
በሸገር ከተማ አስተዳደር በርካታ መምህራን የሥራ ማቆም አድማ ላይ ናቸው