በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ብሔራዊው ቅርስ የጉለሌው ሼኽ ኦጀሌ ቤተ መንግሥት በመፍረስ አፋፍ ላይ ነው


ብሔራዊው ቅርስ የጉለሌው ሼኽ ኦጀሌ ቤተ መንግሥት በመፍረስ አፋፍ ላይ ነው
please wait

No media source currently available

0:00 0:09:14 0:00

ብሔራዊው ቅርስ የጉለሌው ሼኽ ኦጀሌ ቤተ መንግሥት በመፍረስ አፋፍ ላይ ነው

ኢትዮጵያ እንደ ሀገር እና እንደ ሀገረ መንግሥት ካላት ረዥም ታሪክ አኳያ፣ ብዙ ቁሳዊ እና መንፈሳዊ የቅርስ ሀብት እንዳላት የታወቀ ነው፡፡

ከእኒኽም ጥቂቶቹን፣ ከብሔራዊ ጸጋነት ባሻገር በዓለም የሚዳሰሱ እና የማይዳሰሱ ቅርሶች ማኅደር ውስጥ፣ የሰው ልጆች ኹሉ ሀብት እንዲኾኑ አስመዝግባለች፡፡

አንዳንዶቹ ደግሞ፣ የቅርስነት ዕሴታቸው እጅግ ከፍ ያለ ቢኾንም፣ በቂ እንክብካቤ አላገኙም፡፡ ሌሎቹም፣ ጭራሹን እንዲጠፉ የተተዉ እስኪመስል ድረስ፣ እንደ ውዳቂ ዕቃ ተረስተዋል፡፡

በዐዲስ አበባ ከተማ በጉለሌ ክፍለ ከተማ የሚገኘው የሼኽ ኦጄሌ አል ሐሰን መኖሪያ የነበረው ግዙፍ ሕንፃ፣ “ለውድመት የተጋለጡ” ከሚባሉ ብሔራዊ ቅርሶች አንዱ ነው፡፡

ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

መድረክ / ፎረም

XS
SM
MD
LG