በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

እነአቡበከር የክሥ መቃወሚያ አቀረቡ፤ የእነአንዱዓለም ይግባኝ ቀረበ፤ የእስክንድር ነጋ ጉዳይ ለተመድ ግብረኃይል ገባ


Freedom Forum
Freedom Forum




የኢትዮጵያዊያን ሙስሊም ማኅበረሰብን ጥያቄ እንወክላለን የሚሉት እነ አቡበከር አህመድ ሞሃመድ አቃቤ ሕግ ያቀረበባቸውን ክሥ ተቃወሙ።

ጉዳያቸው የቀረበለት ፍርድ ቤት የማየት መብት እንደሌለው ገለፁ።

በእነ አንዱዓለም አራጌና እስክንድር ነጋ የክሥ መዝገብም የይግባኝ አቤቱታ ቀርቧል።
አንዱዓለም አራጌ
አንዱዓለም አራጌ

በከፍተኛው ፍርድ ቤት በሽብር ፈጠራና ብሔራዊ ጥቅምን አሣልፎ በመስጠት ወንጀለኛ ያላቸውን ጋዜጠኛና የፖለቲካ ተቃዋሚዎች አቤቱታ አቃቢ ህግ መልስ እንዲሰጥበት ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።
ፍሪደም ናው
ፍሪደም ናው

በሌላ በኩል ለህሊና እስረኞች የሚሟገተው ፍሪደም ናው “Freedom Now” የሚባለው ድርጅት የእስክንድር ነጋን ጉዳይ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ያላግባብ የታሠሩ ሰዎችን ጉዳይ ለሚያጠናው ግብረኃይል ማቅረቡ ታወቀ።
እስክንድር ነጋ
እስክንድር ነጋ

ግብረኃይሉ በቀረበለት መመልከቻ ላይ በመጭው ሚያዝያ ውሣኔ እንደሚሰጥ ይጠበቃል።

የድርጅቱን ሥራ አስኪያጅ ዘጋቢያችን መለስካቸው አምሃ አዲስ አበባ ላይ አነጋግሯቸዋል።

ዘገባዎቹን ያዳምጡ፡፡

please wait

No media source currently available

0:00 0:09:22 0:00
ቀጥተኛ መገናኛ
XS
SM
MD
LG