አዲስ አበባ —
በዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም ላይ የሥነ-ምግባር ምርመራ እንዲያደርግ ኢትዮጵያ በደብዳቤ ጠየቀች።
የኢትዮጵያ መንግሥት ለቦርዱ በጻፈው ደብዳቤ "የህወሓት ንቁ አባል እና ደጋፊ ሆነው ቀጥለዋል" ያላቸው ዶ/ር ቴድሮስ፣ “ጽ/ቤታቸውን የፖለቲካ ጥቅማቸውን ለማራመድ እየተጠቀሙበት ነው” ሲል ከሷል፡፡
የዓለም ጤና ድርጅት ወደ ትግራይ ክልል መድኃኒቶችን እንዳያስገባ በኢትዮጵያ መንግሥት ተከልክሏል በማለት ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም ሰሞኑን የኢትዮጵያ መንግሥትን መውቀሳቸውን ተከትሎ ነው ክሱ የቀረበው፡፡
ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያገኛሉ።