በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ቆይታ ከኢትዮጵያ አየር ኃይል አዛዥ ጋር


የኢትዮጵያ አየር ኃይል ዋና አዛዥ ሜጄር ጄነራል ይልማ መርዳሳ
የኢትዮጵያ አየር ኃይል ዋና አዛዥ ሜጄር ጄነራል ይልማ መርዳሳ

ህወሓት ትናንት ሌሊት ወደ ባህርዳር የተኮሳቸው ሮኬቶች ምንም ዓይነት ጉዳት አለማድረሳቸውን የኢትዮጵያ አየር ኃይል ዋና አዛዥ ሜጄር ጄነራል ይልማ መርዳሳ አስታወቁ። ሮኬቶቹ ከየት እንደተተኮሱ እናውቃለን ያሉት ዋና አዛዡ ያረፉትም በገበሬ ማሳ ላይ ነው ሲሉ ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል።

እንደ ሜጄር ጀነራሉ ገለፃ በህወሓት እጅ የነበሩ ሮኬቶች አየር ኃይሉ ከዚህ ቀደም ባካሄዳቸው ድብደባዎች ወድመዋል። ህወሓት አሁን የተኮሳቸውም በኮንትሮባንድ እና በተለያየ መንገድ ያስገባቸው እና በየጉድጓዱ የደበቃቸው ናቸው ብለዋል።

የኢትዮጵያ አየር ኃይል እየወሰዳቸው ባሉ እርምጃዎች ሲቪሎች ተጎድተው እንደማያውቁ የገለፁት ዋና አዛዡ ህወሓት በዚህ ረገድ የሰነዘራቸውን ውንጀላዎችም አጣጥለዋል።

ባህር ዳር የወደቁት ሮኬቶች
please wait

No media source currently available

0:00 0:01:06 0:00

በሌላም በኩል ወደ ባህርዳር የተተኮሱት ሮኬቶች ጉዳት አለማድረሳቸውን እና ያረፉትም ማሳ ላይ መሆኑን የዓይን እማኞችም ለአሜሪካ ድምፅ አረጋግጠዋል።

ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምጽ ፋይል ያድምጡ፡፡

ቆይታ ከኢትዮጵያ አየር ኃይል አዛዥ ጋር
please wait

No media source currently available

0:00 0:08:00 0:00


XS
SM
MD
LG