በሚያናማር በእገታ ሥር ቆይተው ወደ ታይላንድ ከተሻገሩ 133 ኢትዮጵያ መካከል 32ቱ ዛሬ ወደ አገራቸው መመለሳቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገልጿል።
በዛሬው ዕለት ከገቡት መካከል አስተያየቱን የሰጠን አንድ ወጣት፣ በምያንማር ለዐሥር ወራት አስከፊ ጊዜ ማሳለፉን ተናግሯል።
ደርሶብኛል ካላቸው አካላዊ የመብት ጥሰቶች በተጨማሪ፣ በሥነ ልቡና ክፉኛ በመጎዳቱ ምክንያት ስሙ እንዳይጠቀስ የጠየቀን ወጣቱ፣ ምንም እንኳን የእርሱ ወደ አገሩ መግባት ቢያስደስተውም፣ ነገር ግን ደስታው ምሉዕ እንዳለሆነ ይገልጻል፡
ከሚያንማር ወደ ታይላንድ የመግባት ዕድል ካገኙት 138 ኢትዮጵያውያን ውስጥ አምስቱ ከዚህ ቀደም ለብዙኅን መገናኛ በሰጡት አስተያየት ምክንያት በሚያንማር ኢሚግሬሽን ትፈለጋላችሁ ተብለው መወሰዳቸውን ከተመላሾቹ መካከል ያነጋገርነው ወጣት አመልክቷል፡፡ እነርሱን ጨምሮ መንግሥት፣ በታይላንድ በካምፕ ውስጥ የሚገኙትን እና በሚያንማር በችግር ላይ ያሉትን ኢትዮጵያውያን ለመታደግ “ከፍተኛ ጥረት ሊያደርግ ይገባል” ሲል ተማፅኗል፡፡