ኢትዮጵያ የሴቶች የንጽሕና መጠበቂያ አቅርቦት ከተጓደለባት ሀገራት ውስጥ አንዷ መኾናን ችግሩን ለመቅረፍ የሚሠሩ ድርጅቶች ይናገራሉ። ከ24 ሚሊየን በላይ የሚሆኑ ሴቶች እና ልጃገረዶችም የንጽህና መጠበቂያ አቅርቦት ችግር እንዳለባቸው ጥናቶች ያመላክታሉ። እጅግ ብዙ ልጃገረዶችም በወር አበባ ወቅት ከትምህርት ቤት ይቀራሉ። በዚኽ ምክኒያትም ከሌሎች ተማሪዎች ያነሰ ውጤት በማስመዝገብ ካለሙበት ሳይደርሱ ይቀራሉ።
"የቲ ፓድስ"ይኽንን መጓደልን ሊያሟላ ይችላል በሚል ዓላማ የተመሰረተ፣ በድጋሚ ጥቅም ላይ የሚውሉ የንጽህና መጠበቂያ ማምረቻ ቦታ ነው።
የድርጅቱ መስራችና የኢትዮጵያ የሴቶች የወር አበባ ጤና እና ንፅህና መጠበቂያ አምራቾች ማኅበር ሥራ አስኪያጅ ፤ የትናየት ሰለሞን በዘንድሮው የዓለም የሴቶች ቀን፤ የሴቶች የንጽሕና መጠበቂያ አቅርቦት ተደራሽነት እና ፍርትሃዊነት ትኩረት ሊሰጠው ይገባል ትላለች።
የትናየት ሰለሞን ከኤደን ገረመው ጋር ቆይታ አድርጋለች።
መድረክ / ፎረም