የፌስቡክ፣ ኢንስታግራም እና ትሬድ ማኅበራዊ ብዙኀን መገናኛዎችን የሚያስተዳድረው ሜታ፣ በማኅበራዊ ትስስር ገጾቹ ላይ የሚተላለፉ ሐሰተኛ መረጃዎችን ለመቀነስ፣ ኤክስ የቀድሞ ቲውተር ማኅበራዊ የትስስር ገጽ እንደሚያደርገው የማኅበረሰብ ማስታወሻዎችን እንደሚጠቀም አስታውቋል።
ሜታ ይህን ያስታወቀው፣ ቀደም ሲል ከሦስተኛ ወገን ጋራ በመተባበር ያካሒድ የነበረውን የመረጃ ማጣራት ባቋረጠበት ወቅት ነው።
ይህ የለውጥ ርምጃ፣ በቅድሚያ አሜሪካ ውስጥ ብቻ ተግባራዊ እንደሚደረግ ለአሜሪካ ድምፅ የገለጸው ሜታ፣ በሌሎች ሀገራት ከመተግበሩ በፊት ተገቢውን ጥናት እንደሚያደርግ አመልክቷል።
ለመኾኑ፣ ሜታ መረጃን ለማንጠር እጠቀምበታለኹ የሚለው ይኸው የማኅበረሰብ ማስታወሻ ምንድን ነው? ሐሰተኛ መረጃን የመዋጋት ዐቅሙስ ምን ያህል ነው? የሚለውን ለመረዳት፦ ስመኝሽ የቆየ በሜኒሶታ ግዛት፣ ሐምሊን ዩኒቨርሲቲ ውስጥ የኮሚዩኒኬሽንና ሚዲያ ጥናት ተመራማሪ እና መምህር የኾኑትን ዶክተር እንዳልካቸው ኀይለ ሚካኤል ጫላን አነጋግረናል።
ዝርዝርሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።
መድረክ / ፎረም