ከአራት አመት በፊት በሚዲያ ተቋም ይሰሩ በነበሩ ጋዜጠኞች የተመሰረተው ሀቅ ቼክ በኢትዮጵያ ሆን ተብለው ሆነ ባለማወቅ የሚሰራጩ መረጃዎችን በማጣራት የሀሰተኛ መረጃዎችን ስርጭት ለመቀነስ ጥረት ሲያደርግ ቆይቷል። በዚህ ተቋም የመረጃ አጣሪዎች አስተባባሪ ሆኖ የሚያገለግለው ኪሩቤል ተስፋዬም የመጀመሪያ ዲግሪውን ያገኘበትን የምህንድስና ሙያ በመተው ሀሰተኛ መረጃ በማህበረሰቡ ውስጥ እያደረሰ ያለውን ጉዳት ለመቀነስ እየሰራ መሆኑን ለአሜሪካ ድምፅ ገልጿል። ስመኝሽ የቆየ ከኪሩቤል ጋር ያደረገችውን ቆይታ ከተያያዘው የቪዲዮ ፋይል ያገኛሉ።
መድረክ / ፎረም